የአማራ መንገድ ሥራዎች ድርጅት አመራሮችና ሰራተኞች በባህዳር ከተማ አስተዳደር ወረብ ቀበሌ በሚገኘው በድርጅቱ አስፓልት ፕላንት ቅጥር ዙሪያ የችግኝ ተከላ አካሄዱ።

የአማራ መንገድ ሥራዎች ድርጅት አመራሮችና ሰራተኞች በባህዳር ከተማ አስተዳደር ወረብ ቀበሌ በሚገኘው በድርጅቱ አስፓልት ፕላንት ቅጥር ዙሪያ የችግኝ ተከላ አካሄዱ።

ሰኔ 15 2015 ዓ.ም በተካሄደው የችግኝ ተከላ ሥነ-ስርዓትም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅን ጨምሮ የሥራ ሂደት መሪዎችና የዋናው ቢሮ ሰራተኞች ተገኝተዋል። የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መብት አድማስ በዕለቱ የተከናወነው የችግኝ ተከላ ስነ ስርዓት ፕሮጀክቶቻችን በሚገኙበት አካባቢ ሁሉ ከአካባቢው አመራርና ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ሊተገበር እንደሚገባ አሳስበዋል።

ችግኞችን በመትከል የአፈር መሸርሸርን ብሎም የአየር ንብረት መዛባትን እንከላከል !!