የአማራ መንገድ ሥራዎች ድርጅት ከዳንግላ ጃዊ መንገድ ስራ ፕሮጀክት ባለድርሻ አካላት ጋር በፕሮጀክቱ አፈጻጸም ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄደ።

ከዳንግላ ጃዊ መንገድ ስራ
የአማራ መንገድ ሥራዎች ድርጅት ከዳንግላ ጃዊ መንገድ ስራ ፕሮጀክት ባለድርሻ አካላት ጋር በፕሮጀክቱ አፈጻጸም ዙሪያ ህዳር 8 2011 ዓ.ም በዳንግላ ከተማ ውጤታማ የምክክር መድረክ አካሄደ።

በውይይቱ የተሳተፉ የመንገዱ ተጠቃሚዎች ድርጅቱ እያካሄደ ያለውን የመንገድ ግንባታ እንቅስቃሴ በአካል በመገኘት እየተከናወነ ያለውን እስከ 75 ሜትር የሚደርሰውን ከፍተኛ የጋራ ቆረጣ ስራ እና የፍንዳታ ስራ በመመልከት አድናቆታቸውን የገለፁ ሲሆን ግንባታውም ተጠናቆ ሙሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚቻላቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።